Home ዜና ዛሬ ማለዳ ቋሚ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ አካሂዶ ነበር።

ዛሬ ማለዳ ቋሚ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ አካሂዶ ነበር።

by admin

በዚህም ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በስቅለት ዕለት በፎኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በቅድስት ድንግል ማርያም ዙሪያ ያስተላለፉትን ትምህርት በተመለከተ ውይይት አድርጓል።

በብፁዕነታቸው የተላለፈውን ትምህርት ዝርዝር ሁኔታን በመመርመርም ውሳኔ ለማስተላለፍ  ይቻል ዘንድ ሁሉም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት በተገኙበት  ለረቡዕ ሚያዝያ 22 ቀን
2017 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።

በሌላ በኩል ፤ በካቶሊክ መሪ በነበሩት ብጹዕ ወቅዱስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ሥርዓተ ቀብር ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በምሥራቅ ጎጃም እና በአውሮፓ ጀርመን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቤተክርስቲያኗን በመወከል እንዲገኙ ተወስኗል።

አጋራ

ተዛማጅ ልጥፎች

Leave a Comment

አንደበት

ለተጠቃሚዎች የቅርብ ጊዜ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፍ ዜና  በማቅረብ ለአንባቢዎች የተሟላ መድረክ የሚሰጥ ዜና ጣቢያ ለአንባቢ ምቹ በይነገጽ እና ሰፋ ያለ የዜና ምድቦች አማካኝነት እንደ ፖለቲካ, ቴክኖሎጂ, መዝናኛ, ስፖርት እና ሌሎችም ባሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል፡፡

ጋዜጣ

አዳዲስ ዜናዎች በቅድሚያ እንዲደርሶት ኢሜሎን በማስገባት ይመዝገቡ

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

@2025 – All Right Reserved.  Powered by Ewenet Communication