Home ዜና ከታሰሩት 14 ባለሙያዎች 7ቱ ሲፈቱ 7ቱ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ ” – የጤና ባለሙያዎች

ከታሰሩት 14 ባለሙያዎች 7ቱ ሲፈቱ 7ቱ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ ” – የጤና ባለሙያዎች

" የ4 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ተከፍሎን ስራ ጀምረናል፤ በወረዳዉ ስራ ሲዘጋ መክፈል የተለመደ ነው !! "

by admin

ከ6 እስከ 9 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ባለመከፈሉ ምክንያት ሥራ ማቆማቸውንና 14 ሰዎች መታሰራቸውን በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ የሚገኘዉ ሀንጣጤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጤና ባለሞያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

ጤና ባለሙያዎቹ ዛራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ከታሰሩት 14 ባለሙያዎች 7ቱ ሲፈቱ 7ቱ አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

ካልተከፈለዉ የ9 ወራት ዉዝፍ ዉስጥ የ4 ወራት ክፊያ መፈጸሙን ተከትሎ ሥራ መጀመራቸውን የገለጹት ባለሞያዎቹ ” የትርፍ ሰዓት ስራ ከቆመ በኋላ ክፍያ መፈፀም በወረዳዉ የተለመደ ጉዳይ ነዉ ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ከታሰሩ 5ኛ ቀናቸዉን የያዙት የታሰሩ የጤና ባለሙያዎች ” እንዲፈቱ በተደጋጋሚ እየጠየቅን ነዉ ያሉት ሰራተኞቹ እስካሁን ግን ግልፅ ምክንያት አልተነገረንም ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሎካ አባያ ወረዳ አስተዳዳሪና ፖሊስ አዛዥን ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።  በጉዳዩ ላይ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን ይገልጻል።

አጋራ

ተዛማጅ ልጥፎች

Leave a Comment

አንደበት

ለተጠቃሚዎች የቅርብ ጊዜ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፍ ዜና  በማቅረብ ለአንባቢዎች የተሟላ መድረክ የሚሰጥ ዜና ጣቢያ ለአንባቢ ምቹ በይነገጽ እና ሰፋ ያለ የዜና ምድቦች አማካኝነት እንደ ፖለቲካ, ቴክኖሎጂ, መዝናኛ, ስፖርት እና ሌሎችም ባሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል፡፡

ጋዜጣ

አዳዲስ ዜናዎች በቅድሚያ እንዲደርሶት ኢሜሎን በማስገባት ይመዝገቡ

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

@2025 – All Right Reserved.  Powered by Ewenet Communication