Home ዜና “አሜሪካ ብቻዋን ቻይናን ልትጋፈጥ አትችልም”

“አሜሪካ ብቻዋን ቻይናን ልትጋፈጥ አትችልም”

by admin

#Ethiopia | አሜሪካ በቻይና የሚነሳውን ፈተና ለመጋፈጥ ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር አለባት ሲሉ የአሜሪካ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኩርት ካምቤል ተናገሩ ፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ ቻይናን በራሷ መግጠም እንደማትችል እና እንደ ጃፓን እና ደቡብ ኮሪያ ካሉ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንዳለባት አመላክተዋል፡፡

ካምቤል፤ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እየተተገበረ ባለው “አሜሪካ ፈርስት” የሚል የውጭ ፖሊሲ ከቻይና ጋር በመጋፈጥ ለውድቀት እየተዘጋጀች ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ዋሽንግተን እና ቤጂንግ ከቴክኖሎጂ እስከ ንግድ ብሎም እስከ ወታደራዊ ብቃት ድረስ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማንኛውንም ፈተና ለመቋቋም የሚያስችል የኢንዱስትሪ እና የቴክኖሎጂ አቅም ያላት ቢሆንም ቻይና በቴክኖሎጂ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በአርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በመርከብ ግንባታ እና በወታደራዊ መስኮች በኩል በርካታ ስራዎች መሰራቷን አንስተዋል፡፡

በመሆኑም ዩናይትድ ስቴትስ ይህንን ፈተና ብቻዋን ልትቋቋም እንደማትችል አንስተው፤ እነዚህን ተግዳሮቶች ለመቋቋም ብቸኛው መንገድ ከአጋሮች ጋር በቅርበት መስራት ነው ብለዋል።

አጋራ

ተዛማጅ ልጥፎች

Leave a Comment

አንደበት

ለተጠቃሚዎች የቅርብ ጊዜ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፍ ዜና  በማቅረብ ለአንባቢዎች የተሟላ መድረክ የሚሰጥ ዜና ጣቢያ ለአንባቢ ምቹ በይነገጽ እና ሰፋ ያለ የዜና ምድቦች አማካኝነት እንደ ፖለቲካ, ቴክኖሎጂ, መዝናኛ, ስፖርት እና ሌሎችም ባሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል፡፡

ጋዜጣ

አዳዲስ ዜናዎች በቅድሚያ እንዲደርሶት ኢሜሎን በማስገባት ይመዝገቡ

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

@2025 – All Right Reserved.  Powered by Ewenet Communication