Home መዝናኛ ለአንድ ሳምንት ተልከው ዘጠኝ ወር የቆዩት ጠፈርተኞች

ለአንድ ሳምንት ተልከው ዘጠኝ ወር የቆዩት ጠፈርተኞች

by admin

#Ethiopia | ለአንድ ሳምንት ተልከው በቴክኒክ ችግር ለዘጠኝ ወራት ጠፈር ላይ ተንሳፈው የቆዩት ጠፈርተኞች ወደ ምድር ተመለሱ

አሜሪካዊያኑ ጠፈርተኞች ባሪ ዊልሞር እና ሱኒታ ዊሊያም በጎርጎሪያኑ ሰኔ 2024 ዓ/ም ለስምንት ቀናት ተልዕኮ ወደ ዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ተጉዘው ነበር።

ነገር ግን ጠፈርተኞቹ የተጓዙበት የስታርላይነር መንኮራኩር በገጠመው የቴክኒክ ችግር በጣቢያው ከዘጠኝ ወራት በላይ እንዲቆዩ ተገደዋል። በዛሬው ዕለት ግን ኬኔዲ የጠፈር ጣቢያ መድረሳቸው ተዘግቧል።

ሁለቱም ጠፈርተኞች ልምድ ያላቸው የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ፤ ከአሁኑ ከተልዕኮ በፊት በመቶዎች የሚቆጠሩ ቀናትን በጠፈር አሳልፈዋል ተብሏል።

በተለይ የስታርላይነር በረራ የመጀመሪያ እና የሙከራ ተልእኮ ስለነበር ለከፋ ሁኔታ ተዘጋጅተው የሰለጠኑ ናቸውም ነው የተባለው።

ያም ሆኖ የናሳ ጠፈርተኞች ባሪ “ቡች” ዊልሞር እና ሱኒታ “ሱኒ” ዊልያምስ ከታሰበው በላይ ጠፈር ላይ በመቆየታቸው የጤና አደጋዎች ሊያጋጥሟቸው እንደሚችል ተነግሯል።

አጋራ

ተዛማጅ ልጥፎች

Leave a Comment

አንደበት

ለተጠቃሚዎች የቅርብ ጊዜ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፍ ዜና  በማቅረብ ለአንባቢዎች የተሟላ መድረክ የሚሰጥ ዜና ጣቢያ ለአንባቢ ምቹ በይነገጽ እና ሰፋ ያለ የዜና ምድቦች አማካኝነት እንደ ፖለቲካ, ቴክኖሎጂ, መዝናኛ, ስፖርት እና ሌሎችም ባሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል፡፡

ጋዜጣ

አዳዲስ ዜናዎች በቅድሚያ እንዲደርሶት ኢሜሎን በማስገባት ይመዝገቡ

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

@2025 – All Right Reserved.  Powered by Ewenet Communication