Home ዜናፖለቲካ ” 4 ኪሎ ቤተመንግስት ዙሪያ ያሉ መንገዶች ከዚህ በኋላ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አገልግሎት ይሰጣሉ ” – የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን

” 4 ኪሎ ቤተመንግስት ዙሪያ ያሉ መንገዶች ከዚህ በኋላ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አገልግሎት ይሰጣሉ ” – የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን

by admin

ከዚህ በኋላ 4 ኪሎ ቤተመንግስት ዙሪያ ያሉ መንገዶች በአንድ አቅጣጫ ብቻ አገልግሎት እንደሚሰጡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።

በመሆኑም ፦

  • ከጥይት ቤት  እስከ ፓርላማ ትራፊክ መብራት፣
  • ከቤተመንግስት ፖርክንግ እስከ ጥይት ቤት
  • ከፓርላማ ትራፊክ መብራት እስከ ሳይንስ ሙዝየም ድረስ ያሉ መንገዶች ቀድሞ ከነበረው ባለሁለት አቅጣጫ መንገድ ወደ አንድ አቅጣጫ መንገድ ተቀይረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳን መስመሮቹ እንደ ቀድሞው ባለ ሁለት አቅጣጫ ሆነው አገልግሎት መስጠታቸውን መቼ ይጀምራሉ ? ሲል ጠይቋል።

በምላሻቸው በአንድ አቅጣጫ እንጂ ወደበፊቱ ተመልሶ በሁለት አቅጣጫ አገልግሎት እንደማይሰጡ ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አስቀድመው ” ለሁለት ቀን ወደ አንድ አቅጣጫ (One way) ተደርገው አገልግሎት ይሰጣሉ ” በሚል ለቲክቫህ  ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ሆኖም  ” ለሁለት ቀን ያልኩት በአንድ አቅጣጫ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎች እና የጎደሉትን የማሟላት ስራ ለመስራት ነው ” ሲሉ መንገዶቹ በቀጣይነትም ባለ አንድ አቅጣጫ መንገድ ሆነው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።

አክለውም ” የትራፊክ ስራ ዳይናሚክ ነው፣ እንደ የአስፈላጊነቱ  በየጊዜው የማሻሻል ስራዎች ሊኖሩ ይችላሉ ” በማለት ጠቁመዋል።

ከዚህ በኃላ ግን መንገዶቹ ባለ አንድ አቅጣጫ ብቻ እንደሆኑ አስገንዝበዋል።

አጋራ

ተዛማጅ ልጥፎች

Leave a Comment

አንደበት

ለተጠቃሚዎች የቅርብ ጊዜ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፍ ዜና  በማቅረብ ለአንባቢዎች የተሟላ መድረክ የሚሰጥ ዜና ጣቢያ ለአንባቢ ምቹ በይነገጽ እና ሰፋ ያለ የዜና ምድቦች አማካኝነት እንደ ፖለቲካ, ቴክኖሎጂ, መዝናኛ, ስፖርት እና ሌሎችም ባሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል፡፡

ጋዜጣ

አዳዲስ ዜናዎች በቅድሚያ እንዲደርሶት ኢሜሎን በማስገባት ይመዝገቡ

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

@2025 – All Right Reserved.  Powered by Ewenet Communication