Home ዜና የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኗን።

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኗን።

by admin

በትግራይ መምህራን ማህበር ጠበቆች የቀረበውና በጦርነቱ ጊዜ ያልተከፈለ የ17 ወራት የመምህራን ደመወዝ ሲመለከት የቆየው ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም ባዋለው ችሎት ውሳኔውን ሰጥቷል።

ተከሳሾቹ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ፣ የፋይናንስ  ቢሮ ፣ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲሁም የገንዘብ/ የፋይናንስ ሚንስቴር ሲሆኑ ጉዳያቸው በሌሉበት ሲታይ ቆይቷል።

ፍርድ ቤቱ የቀረበለት ክስ መርምሮ የመምህራኑ የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኖ ፋይሉ ወደ መዝገብ ቤት መልሶታል። 

የፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንደሚቀበሉትና እንዳረካቸው የተናገሩት አስተያየት ሰጪ መምህራን ውሳኔው ቶሎ በመተግበር በከፋ ሁኔታ የሚመገኙ መምህራን መታደግ ይገባል ብለዋል።

ተከሳሾቹ ውሳኔው በማስመልከት እስካሁን ያሉት ነገር የለም።

መምህራን ያካተተ የ17 ወራት ያልተከፈለ የመንግስት ሰራተኞች ውዙፍ ደመወዝ የመከፈል ጥያቄ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የጀመረ ነው።

በቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዚያዊ አስተዳደር ጉዳዩ በፍርድ ቤት እንዳይታይ የሚከልክል መምሪያ እስከማውጣት ደርሶ ነበር።

አጋራ

ተዛማጅ ልጥፎች

Leave a Comment

አንደበት

ለተጠቃሚዎች የቅርብ ጊዜ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፍ ዜና  በማቅረብ ለአንባቢዎች የተሟላ መድረክ የሚሰጥ ዜና ጣቢያ ለአንባቢ ምቹ በይነገጽ እና ሰፋ ያለ የዜና ምድቦች አማካኝነት እንደ ፖለቲካ, ቴክኖሎጂ, መዝናኛ, ስፖርት እና ሌሎችም ባሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊ ዜናዎችን ያቀርባል፡፡

ጋዜጣ

አዳዲስ ዜናዎች በቅድሚያ እንዲደርሶት ኢሜሎን በማስገባት ይመዝገቡ

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

@2025 – All Right Reserved.  Powered by Ewenet Communication